የኤርትራ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፋሲል ከነማ ያቀረበውን የወዳጅነት ጨዋታ ጥያቄ ተቀበለ

Daily Ethiopian News, አዳዲስ ዜናዎች።
Forum rules
** When you post a News please include the Source link.
For More Ethiopian News please visit the Home Page
http://ethiopiaforums.com/
selam sew
Leader
Leader
Posts: 692
Joined: 08 Feb 2011 11:14
Contact:

የኤርትራ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፋሲል ከነማ ያቀረበውን የወዳጅነት ጨዋታ ጥያቄ ተቀበለ

Unread post by selam sew »

የኤርትራ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፋሲል ከነማ ያቀረበውን የወዳጅነት ጨዋታ ጥያቄ ተቀበለ
Image

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኤርትራ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፋሲል ከነማ በኤርትራ ፕሪምየርሊግ ውስጥ ከሚጫወት የእግር ኳስ ክለግ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ያቀረበውን ጥያቄ ተቀበለ።

ፌዴሬሽኑ በፃፈው የመልስ ደብዳቤም የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ በኤርትራ ፕሪምየር ሊግ ውስጥ ለመጫወት ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን አስታውቋል።

የኤርትራ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአስመራ ላይ በቅርቡ ለማካሄድ የተሰበውን የወዳጅነት የእግር ኳስ ጨዋታ ለማስተናገድ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ መጀመሩንም አስታውቋል።

የወዳጅነት የእግር ኳስ ጨዋታው የሚካሄድበት ቀንም በቅርቡ እንደሚያስታውቅ ነው ፌዴሬሽኑ ለፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ በላከው ደብዳቤ ያስታወቀው።

የኤርትራ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ያቀረበው የወዳጅነት የእግር ኳስ ጥያቄም የሀገራቱ መሪዎች ሰላምን ለማስፈን የጀመሩትን ስራ የሚያጠናክር ነው ሲልም አድንቆታል።

Image

የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ በኤርትራ ፕሪምየር ሊግ ከሚጫወት ክለብ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ባሳለፍነው ሰኔ 30 2010 ዓ.ም ለኤርትራ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄ ማቅረቡ ይታወሳል።
Post Reply

Return to “Ethiopian Daily News .. ኢትዮ ዜናዎች”