ሰላም ሰላም!

Forum rules
No cursing, bad language and offend other users !
No pornographic images or links!
This forum monitored regularly. We will BAN users without warning for not obeying rules.
እባክዎ የፎረሙን ህጎች ያክብሩ::
Jigsa
Starter
Starter
Posts: 21
Joined: 13 Feb 2013 01:27
Contact:

ሰላም ሰላም!

Unread post by Jigsa »

የተከበራችሁ የጀምጀም ተወላጆችና ወዳጆች!
በ አዶላ ኮፊ ኤንድ ቲ ሩም የተዋወቅናቸው ወዳጃችን ምስጋና ይድረሳቸውና ይሄው በዚህ መድረክም ብቅ ለማለት ችያለሁኝ፡፡ እኔ አቶ ጅግሳ ገበያ ክፍል ተወልጄ ፈረንጅ ውሃና ካምቦ አድጌ የአዶላ አባዜ ልለቅህ ብሎኝ ነጌሌ ቦረናና አዶላ መካከል ስወዛወዝ ጠጉሬ ላይ የማላውቀው ነጣ ነጣ ያለ ጸጉር ነገር ወጣብኝ፡፡ ወጉለበቴም ደከም እያለ አይኔም እንደወትሮው አልሆን ማለት ጀምሯል፡፡
አንዱ ወዳጃችን ማን ነበር ስለ አቶ ቢሉ ባነታ አንስቶ ኢህአዴግ ወደ አዶላ ሲገባ ጦር ወደ ሃገረ ሰላም ይዞ መዝመቱን ያስታወሰኝ፡፡አረ እኔ ራሴ ነበርኩኝ አዶላ ስታዲየም ላይ ግንባሩ ሲቋቋም… ወደፊት ጫር ጫር አድርጌ አወጋችኋለው ይህ ፎረም እንዲህ ያለ ነገር ፖስት ማድረግ ከፈቀደ!
ነገር ግን ይህ ፎረም ትዝታን ከማውጋት በሻገር ስለ ሀገራችን ፣ ት/ቤታችን… ወዘተ መልሶ መቋቋም የምናወጋበት (በዘመኑ ቋንቋ) ልማታዊ መድረክ ብናደርገው! ቅቅቅቅቅቅ! ቸር ሰንብቱልኝማ!
Post Reply

Return to “የጀምጀም ልጆች መገናኛ”