የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Forum rules
No cursing, bad language and offend other users !
No pornographic images or links!
This forum monitored regularly. We will BAN users without warning for not obeying rules.
እባክዎ የፎረሙን ህጎች ያክብሩ::
Wadera
Posts: 4
Joined: 01 Jan 2012 17:18
Contact:

የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by Wadera »

ሰላም ለክብረ መንግስት፣ ለቦሬ፣ ለአገረ ሰላም፣ ለሻኪሶ፣ ለዘንባባ ውሃ፣ ለዋደራ፣ ለገናሌ፣ ለጨንቤ፣ ለኢርባ ሙዳና ለመላው የአካባቢው ልጆች እንደምን ሰነበታችሁ? በየጊዜው የምንገናኝበት ዋርካ ጄነራል አጸያፊ ጽሁፎችን ከማስነበቡም በላይ አንዳንድ ግለሰቦችም አልፈው ተርፈው የሌሎችን ሃይማኖት በማጥላላት አምላካችንን ሁሉ ሳይቀር በማዋረድ የሚያካሄዱት ተግባር በጣም የሚዘገንን ሆኖ ስላገኘሁት ወደዚያ ቤት መሄዱ በጣም ስላስጠላኝ ይህን ቤት ለማግኘት በመቻሌ ደስ ብሎኛል።

የዋርካ ዌብሳይት ሃላፊዎች ብልግና የተሞላባቸውን ጽሁፎች እንዲያስወግዱ ጸሐፊዎቹንም ከዚህ ዓይነት ተግባር እንዲቆጠቡ እንዲነግሩዋቸው በተደጋጋሚ ቢጠየቁም ጥያቄዎቹን ሁሉ ስላልተቀበሉ ሌሎቻችን ያለን ምርጫ ከዚያ ቤት መውጣት ብቻ ነው። ስለዚህ ይህን ገጽ እዚህ ጀምረን ስለ አደግንበት አካባቢና ስለ ሌሎችም ተዛማች ጉዳዮች እዚህ እየተገናኘን እንድንወያይ በአክብሮት እጠይቃለሁ።

አመሰግናለሁ

ዋደራ (የዋርካው አንፈራራ)
Wadera
Posts: 4
Joined: 01 Jan 2012 17:18
Contact:

Re: የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by Wadera »

ስላም ለሁላችሁ

ሞፊቲ በዋርካ ላይ የጻፍከውን አነበብኩት፣ በጣም ደስ ብሎኛል፣ እዚያ ያለህን ስም እንደያዝክ እዚህም መመዝገብ የምትችል ይመስለኛል። አስተዳዳሪዎቹም የ "እንክዋን ደህና መጣህ" መልክት ልከውልኛል፣ እዚህ ሁሉ ነገር በሥርዓት እንደሚካሄድም አረጋግጠውልኛል። ስለዚህ እባካችሁ እዚህ እየተመዘገባችሁ ያቋረጥነውን ውይይት እንቀጥል።

ቻው ላሁኑ።
ራስብሩ
Starter
Starter
Posts: 23
Joined: 03 Jan 2012 09:45
Contact:

Re: የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by ራስብሩ »

ሰላም ጤና ይስጥልኝ
ወደአዲሱ ቤታችን ለመምጣት መንገዱ ቀላል ቢሆንም በአማርኛ ቶሎ ለመጻፍ ቀላል አልነበረም
ወደኋላ ተመልሼ በፍለጋ ነው ያገኘሁት : ያም ሆነ ይህ ወንድማችን ዋደራ ከልብ የመነጨው ምስጋናችን ይድረስህ
የፈጠረንን አምላክ እንዲህ ባለ ፍጹም ባልጌና ጸያፍ ቃላት ሲሰደብ ማየት ራሱ በውነት አለመታደል ነው
ዋርካዎች (ባለቤቶቹ) ምን አይነት ልቦና እንዳላቸው በውነት ግራ ነው የሚገባኝ :
አንደኛ በዌብ ሳይቱ ላይ በትክክል የተቀመጠውን መመሪያ አላስከበሩም እነሱም አላከበሩም
ሁለተኛ ይሄ ጉዳይ የህብረተሰቡን መብት የሚነካና እና ሃይማኖትን የሚነቅፍ መሆኑን በሚገባ ያውቃሉ
ሶሰተኛ ተደጋገሞ ተነግሮአቸው ሊያርሙ አለቻሉም ................
ሰለዚሀ በዚህ ሁኔታ ላይ አብረን መገኘት የለብንም ::

ወራ ጀምጀምቱ እንግዲሀ አዲስ ቤት ሰርተናል
ጎራ በሉ

የናንተው ራስብሩ
Wadera
Posts: 4
Joined: 01 Jan 2012 17:18
Contact:

Re: የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by Wadera »

ሰላም ራስብሩ እንኳን ደህና መጣህ
አማርኛው እውነትም በጣም ቆንጆ ፊደሎች አሉት::ግን ወደዚያ የሚሸጋገርበትን መንገድ ለማግኘት ያስችግር ይሆናል ለማንኛውም ልሞክር::
Wadera
Posts: 4
Joined: 01 Jan 2012 17:18
Contact:

Re: የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by Wadera »

"በአማርኛ ይጻፉ" የሚለውን ስትጫኑ አንድ መጻፊያ ክፍት ቦታ ይሰጣል: ከዚያም በክፍቱ ቦታ ላይ ጽፎ ያንን ኮፒ አድርጎ ዋናው መልክት መላኪያው ላይ መለጠፍ ማለት ፔስት ማድረግ ነው::
ሞፊቲ
Jogger
Jogger
Posts: 33
Joined: 03 Jan 2012 14:19
Contact:

Re: የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by ሞፊቲ »

ሰላም ሰላም ::
Last edited by ሞፊቲ on 03 Jan 2012 14:41, edited 1 time in total.
ሞፊቲ
Jogger
Jogger
Posts: 33
Joined: 03 Jan 2012 14:19
Contact:

Re: የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by ሞፊቲ »

ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን::

ዋደራ ቤታችንን አደራጅተህ ስለጠበከን ከልብ አመሰግናለሁ::
የ አማርኛውን ፊደል በቀላሉ እንደዋርካ የምንጽፍበት መንገድ ቢኖር መልካም ነው::ትንሽ ግራ ያጋባል::ለምንኛውም ስንለምደው ይቀል ይሆናል::
ሆዴን ባር ባር ብሎታል:: ያም ቢሆን ያንን ሁሉ የተካበት የጽሁፍ ሃብት ወደዚህ የምንስብበት መንገድ ቢኖር መልካም ነው እላለሁ::

በሉ እንበርታ!
ሰላም ሁኑልኝ::
አንፈራራ
Runner
Runner
Posts: 50
Joined: 03 Jan 2012 12:51
Contact:

Re: የጀምጀም ልጆች መገናኛ

Unread post by አንፈራራ »

ወደ ተለመደው ስሜ ተመልሻለሁ:: አሁንም "አንፈራራ" ነኝ:: ዋደራ! አመሰግናለሁ ቤቱን ስለከፈትክልን: አሁን ግን ወደ ቤትህ ተመለስ:: :)
Post Reply

Return to “የጀምጀም ልጆች መገናኛ”