VERY FUNNY AMHARIC JOKE.
Posted: 11 Mar 2010 16:52
ከአቶ ገላጋይ ዳኘው
አሜሪካን ለምትገኚው ከይሲዋ ባለቤቴ ለወ/ሮ ፈለቀች በልሁ
ይድረስ ለጉደኛዋ ከይሲ የሰይጣን ቁራጭ ለሆንሺው ለፈለቀች፡- እዛ
ቁልቢ ገብርኤል አንቺን ያገኘሁበትን ቀን እየረገምኩ እሱ መልአኩ ግን
የስራሺን እንዲሰጥሽ ጠዋት ማታ ከመማፀኔም ሌላ ሳልሞት ያንቺን ጉድ
እንዲያሳየኝ ከድሬዳዋ ቁልቢ የእግር ጉዞ ለማድረግ ተስያለሁ፡፡
የአሜሪካንን አገር ግሪን ካርድ እንዳንቺ አገኛለሁ ብዬ በሌለኝ ደሜ
ሦስት ብልቃጥ ሙሉ ደም ለምርመራ ሰጥቼ እዚህ ግቢዬ ውስጥ
የተተከለውን የሣተላይት ዲሽ የሚያክል ጆሮ ያለው ዶክተሩ ልጅሽ የእኔ
ልጅ እንዳልሆነ ያው የአሜሪካን አምባሲ ዲ.ኤን.ኤ. በተባለው የደም
ምርመራ አረጋግጦ ጉድሽን አፈላው፡፡
ያ ጭንቅላታም ልጅሽ መቼ በጤናው ከልጆቼ ሁሉ ተለይቶ ተፈጠረ፡፡
አሁንማ ልብ ብዬ ሳስበው የዛ የዘበኛዬን የውቃው ልጅ እንደሆነ
ገብቶኛል፡፡ መቼ ማእረግ ይወድልሻል፤ አንቺ ማእረገ ቢስ፤ በየሜዳው
ስትባልጊ ይኼው በአርባ ዓመቱ ጉድሽ እንደ ወ/ሮ አልማዝ ያልተወቀጠ
ቡና ተንተከተከልሽ፡፡
ይኽን ጉድሽን አሜሪካን አምባሲ ከሰጠኝ ደብዳቤ ጋር ፎቶግራፍሽን
አያይዤ ጋዜጣ ላይ አወጣዋለሁ፡፡ ደግሞ አገር አለኝ፤ ቤት ንብረት አለኝ
ብለሽ እዚህ አገር እንኳን እስከነፍስሽ ሬሳሽ ዝር እንዳይል፡፡ ይኽን
ጉድሽን ለሀገር ለሠፈሩ፤ ለእድርሽ ሳይቀር ተናግሬ ቀባሪ አሳጣሻለሁ፡፡
እዛው ፈረንጅ አገር ሬሳሽን ያቃጥሉት፤ እንዲህ አንጀቴን
እንዳቃጠልሽኝ፡፡
ደግሞ ያንቺ ጉድ ማለቂያ ስለሌለው እነዚህን የቀሩትን ዘጠኙ
ልጆችሽን አሰልፌ ነገ በጠዋት አስመረምርልሻለሁ፡፡ አርባ ዓመት ሙሉ
ልጄ ነው ብዬ አሳድጌ፤ አስተምሬ፤ ፈረንጅ አገር ልኬ ለካስ የዘበኛዬ
የውቃው ልጅ ኖሯል? አንቺ ጉደኛ ብቻ እዚች አገር እግርሽን አንስተሸ
እንዳትመጪ! ብሞት እንኳን ቀብሬ ላይ እንዳትቆሚ ለንስሃ አባቴ
ኑዛዜዬን እናገራለሁ፡፡
የአባት የእናቴ አምላክ አንጀትሽን የእኔ አንጀት እንዳረረ ያሳርርሽ፡፡
አብረን እንቀበርበታለን ብዬ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ያሰራሁትን መቃብር
ቤት መነኩሴ አስቀብርበታለሁ፡፡
ገላጋይ ዳኘው
አዲስ አበባ አሮጌው አውሮፕላን ማረፊያ
ነፍስሽን ያሳርፈውና! ከይሲ!
23 ጥር 2፼2 ዓ.ም. ናፍቆት Iትዮጵያ
“ጉድ ፈላ!”
በአልሣቤት ገበየሁ
2ኛ ዓመት ቁጥር ፴
በአልሣቤት ገበየሁ
አሜሪካን ለምትገኚው ከይሲዋ ባለቤቴ ለወ/ሮ ፈለቀች በልሁ
ይድረስ ለጉደኛዋ ከይሲ የሰይጣን ቁራጭ ለሆንሺው ለፈለቀች፡- እዛ
ቁልቢ ገብርኤል አንቺን ያገኘሁበትን ቀን እየረገምኩ እሱ መልአኩ ግን
የስራሺን እንዲሰጥሽ ጠዋት ማታ ከመማፀኔም ሌላ ሳልሞት ያንቺን ጉድ
እንዲያሳየኝ ከድሬዳዋ ቁልቢ የእግር ጉዞ ለማድረግ ተስያለሁ፡፡
የአሜሪካንን አገር ግሪን ካርድ እንዳንቺ አገኛለሁ ብዬ በሌለኝ ደሜ
ሦስት ብልቃጥ ሙሉ ደም ለምርመራ ሰጥቼ እዚህ ግቢዬ ውስጥ
የተተከለውን የሣተላይት ዲሽ የሚያክል ጆሮ ያለው ዶክተሩ ልጅሽ የእኔ
ልጅ እንዳልሆነ ያው የአሜሪካን አምባሲ ዲ.ኤን.ኤ. በተባለው የደም
ምርመራ አረጋግጦ ጉድሽን አፈላው፡፡
ያ ጭንቅላታም ልጅሽ መቼ በጤናው ከልጆቼ ሁሉ ተለይቶ ተፈጠረ፡፡
አሁንማ ልብ ብዬ ሳስበው የዛ የዘበኛዬን የውቃው ልጅ እንደሆነ
ገብቶኛል፡፡ መቼ ማእረግ ይወድልሻል፤ አንቺ ማእረገ ቢስ፤ በየሜዳው
ስትባልጊ ይኼው በአርባ ዓመቱ ጉድሽ እንደ ወ/ሮ አልማዝ ያልተወቀጠ
ቡና ተንተከተከልሽ፡፡
ይኽን ጉድሽን አሜሪካን አምባሲ ከሰጠኝ ደብዳቤ ጋር ፎቶግራፍሽን
አያይዤ ጋዜጣ ላይ አወጣዋለሁ፡፡ ደግሞ አገር አለኝ፤ ቤት ንብረት አለኝ
ብለሽ እዚህ አገር እንኳን እስከነፍስሽ ሬሳሽ ዝር እንዳይል፡፡ ይኽን
ጉድሽን ለሀገር ለሠፈሩ፤ ለእድርሽ ሳይቀር ተናግሬ ቀባሪ አሳጣሻለሁ፡፡
እዛው ፈረንጅ አገር ሬሳሽን ያቃጥሉት፤ እንዲህ አንጀቴን
እንዳቃጠልሽኝ፡፡
ደግሞ ያንቺ ጉድ ማለቂያ ስለሌለው እነዚህን የቀሩትን ዘጠኙ
ልጆችሽን አሰልፌ ነገ በጠዋት አስመረምርልሻለሁ፡፡ አርባ ዓመት ሙሉ
ልጄ ነው ብዬ አሳድጌ፤ አስተምሬ፤ ፈረንጅ አገር ልኬ ለካስ የዘበኛዬ
የውቃው ልጅ ኖሯል? አንቺ ጉደኛ ብቻ እዚች አገር እግርሽን አንስተሸ
እንዳትመጪ! ብሞት እንኳን ቀብሬ ላይ እንዳትቆሚ ለንስሃ አባቴ
ኑዛዜዬን እናገራለሁ፡፡
የአባት የእናቴ አምላክ አንጀትሽን የእኔ አንጀት እንዳረረ ያሳርርሽ፡፡
አብረን እንቀበርበታለን ብዬ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ያሰራሁትን መቃብር
ቤት መነኩሴ አስቀብርበታለሁ፡፡
ገላጋይ ዳኘው
አዲስ አበባ አሮጌው አውሮፕላን ማረፊያ
ነፍስሽን ያሳርፈውና! ከይሲ!
23 ጥር 2፼2 ዓ.ም. ናፍቆት Iትዮጵያ
“ጉድ ፈላ!”
በአልሣቤት ገበየሁ
2ኛ ዓመት ቁጥር ፴
በአልሣቤት ገበየሁ