የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ

by

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ Ethiopian breaking news

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ዛሬ መደበኛ ስብሰባውን ያደረገው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ ወሰነ።

ምክር ቤቱ በስብሰባው የሀገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ ገምግሟል።

አሁን ላይም በሀገሪቱ ስርዓት ሰፍኖ ሰላምና መረጋጋት በመመለሱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍፁም አረጋ አስታውቀዋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የሚጠይቅ ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ እንዲፀድቅ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልኳል።

ረቂቅ የውሳኔ ሀሳቡ በምክር ቤቱ ሲፀድቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳል ተብሎ ይጠበቃል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የካቲት 23 2010 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የካቲት 9 ቀን 2010 ዓመተ ምህረት ለስድስት ወራት ያወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማፅደቁ ይታወሳል።

ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 93 ንዑስ አንቀጽ 1 (ሀ) መሰረት በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ በምክር ቤቱ ያፀደቀው።

በህገ መንግስቱና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ ላይ የተጋረጠውን ይህን አደጋ በመደበኛው የህግ ማስከበር ስርዓት ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከማይቻልበት ደረጃ ላይ መድረሱንና ህገ መንግስታዊ ስርአቱን ለመጠበቅ የሚያስችል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማውጣት በማስፈለጉ ነበር የታወጀው።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባው የሀገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ አሁን ላይ በሀገሪቱ ስርዓት ሰፍኖ ሰላምና መረጋጋት በመመለሱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ ወስኗል።


AddisNews is not responsible for the contents or reliability of any other websites to which we get contents from and provide a link and do not necessarily endorse the views expressed by them.

Click Here to Read More on AddisNews

Related Posts

Leave a Comment